Friday, September 11, 2015

የ2008 ዓ.ም የመሰናዶ ትምህርት የመግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ

ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ2008 ዓ.ም የመሰናዶ ትምህርት የመግቢያ ነጥብ ይፋ ማድረጉን አስታውቋል።

በዚህም ለመደበኛ እና የማታ ተማሪዎች ለወንዶች 2 ነጥብ 71 እና በላይ ለሴቶች 2 ነጥብ 43 እና ከዚያ በላይ ሆኗል።
የታደጊ ክልሎችና የአርብቶ አደር አካባቢ ተማሪዎች ለወንዶች 2 ነጥብ 43 እና ከዚያ በላይ ለሴቶች 2 ነጥብና 14 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ለአይነስውራንና መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለወንዶች 2 ነጥብ 14 እና ከዚያ በላይ ለሴቶች 2 ነጥብ እና ከዚያ በላይ ሆኗል።
የግል ተፈታኞች ደግሞ ለወንዶች 3 ነጥብ 29 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ለሴቶች 3 ነጥብ እና ከዚያ በላይ መሆኑን ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ገልጿል።

No comments:

Post a Comment